የሀገር ውስጥ ዜና

ወደ ቻይና ከሚላኩ የወጪ ምርቶች ጋር በተያየዘ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ውይይት ተካሄደ

By Feven Bishaw

March 18, 2022

አዲስ አበባ፣መጋቢት 9፣2014 (ኤፍ ቢሲ) ወደ ቻይና ከሚላኩ የወጪ ምርቶች ጋር በተያያዘ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ የበይነ-መረብ ውይይት የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ተካሂዷል።

በውይይቱ አዲሱ ህግ ድንጋጌዎችና በላኪ ድርጅቶች ላይ እየፈጠረ ያለው ተፅዕኖ በስፋት የተነሳ ሲሆን፥ ችግሩንም ለመቅረፍ በጊዜያዊነትና በዘለቄታዊነት ይረዳሉ የተባሉ የመፍትሄ ሀሳቦችም ቀርበዋል።