አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ የኮንግረስ አባላት አዘጋጅነት በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ ለመጣል በሂደት ላይ ያለው ኤች አር 6600 ረቂቅ አዋጅ እንዳይጸድቅ ለማድረግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባው ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተናገሩ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉትና በካናዳ የሚኖሩት ዮሃንስ አየለ እና ኑሮውን በአዲስ አበባ ያደረገው ወጣት መላኩ አስማማው እንዳለው÷ ረቂቅ ህጉ ባለስልጣናትን ሳይሆን በደሃው ኢትዮጵያዊ ላይ የሚያሳርፈው ጉዳት ከፍ ያለ ነውና ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ ልክ መንቀሳቀስ ይገባል ነው ያለው።