አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ተከሳሾች ጌታነህ አቸነፍ እነ ሞገስ ሙሉጌታ ከሌላ ካልተያዘ ግብረ አበራቸው ጋር በመሆን በፈፀሙት የውንብድና ወንጀል በዓቃቢ ህግ ክስ ተመስርቶባቸው በ5 ዓመት ከ4 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው፡፡
ግለሰቦቹ በእስራት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32/1/ሀ/ እና 670 ስር የተመለከተውን በመተላለፍ መሆኑ ተመልክቷል።