ዓለምአቀፋዊ ዜና

ምዕራባውያን ለዩክሬን የሚያደርጉትን ድጋፍ ለማጠናከር ተስማሙ

By Feven Bishaw

March 25, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምዕራባውያን መሪዎች ለዩክሬን የሚያደርጉትን የተለያዩ ድጋፎች ለማጠናከርና ለማስፋፋት ተስማምተዋል፡፡

የምዕራባውያን የቡድን 7 ሀገራት መሪዎች በብራሰልስ ባካሄዱት ስብሰባ፥ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ያደረገችውን ወረራ እንደሚያወግዙ እና ለዩክሬን ወታደራዊና ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረግ መስማማታቸው ተገልጿል፡፡