አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጥራት በታች የሆኑ 130 የሚሆኑ ማሸነሪዎች ከስራ እንዲወጡ እና አምስት የህንጻ ግንባታ ስራዎች በጥራት ጉድለት ምክንያት እንዲፈርሱ መደረጉን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ገለጸ፡፡
ባለስልጣኑ ከአጋር አካላት ጋር በደሴ ከተማ ዘርፉን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እየመከረ ሲሆን፥ በኮንስትራክሽን ዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ሁሉም አካላት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡