አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 16 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከደሴ ወደ ሰቆጣ ሲጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ አንድ ህጻን ልጅን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተሳፋሪዎች ህይወታቸው ሲያልፍ 37 ተሳፋሪዎች ቆስለው ላሊበላ ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ።
ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ ከደሴ ከተማ ተነስቶ ወደ ሰቆጣ ሲጓዝ የነበረና ከ43 ሰው በላይ የጫነ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላሊበላ ከተማን አለፍ ብሎ ሰኞ ገበያ ከምትባል አካባቢ በመገልበጡ አደጋው መድረሱን ከዋግ ኸምራ ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡