የሀገር ውስጥ ዜና

የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

By Feven Bishaw

March 27, 2022

አዲስ አበባ፣መጋቢት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን “ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት” በሚል መሪ ሀሳብ ማካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የፓርቲው አባላት እና አመራሮች ተሳትፍዋል።