የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ሰባት ወራት 24 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ

By Tibebu Kebede

February 27, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ሰባት ወራት 24 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል።

ቢሮው በቀጣይ በሚያደርገው የገቢ ማሻሻያ የታክስ ንቅናቄ መሪ እቅድ ዙሪያ ከሚመለከታችው የመንግስት አካላትና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር እየመከረ ነው።