የሀገር ውስጥ ዜና

የግብርና ሜካናይዜሽን የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈረመ

By Tibebu Kebede

February 28, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የግብርና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ እና ኢትዮሊዝ ከተሰኘ ድርጅት ጋር ግብርናን ሜካናይዝድ ለማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱን በግብርና ሚኒስቴር የእርሻ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሳኒ ረዲ፣ የኢትዮሊዝ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቄ እና የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዶክተር ጪምዶ አንጫላ ተፈራርመውታል።