የሀገር ውስጥ ዜና

የሰብአዊ ድጋፍ የጫኑ 30 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ለመጓዝ ዝግጁ መሆናቸው ተገለጸ

By Feven Bishaw

April 20, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ምግብ ፕሮግራም የሰብአዊ ድጋፍ የጫኑ 30 ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ለመጓዝ ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቀ።

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ክሌር ኔቪል እንደገለጹት፥ ለአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ የሚያስፈልጉ አቅርቦቶችና አልሚ ምግቦችን የያዙ 30 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ለመጓዝ ዝግጁ ሆነዋል።