የሀገር ውስጥ ዜና

የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ለፋሲካ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

By Mekoya Hailemariam

April 23, 2022

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።ትንሳኤው ፍቅር ጥላቻን፤ እውነት ሃሰትን፤ ደግነት ክፋትን ያሸነፉበት በዓል ነው ብለዋል።

በአሉ ሰላም፣ ፍቅር፣ አብሮነት፣ ተስፋ ፣ ይቅርታ የሚያብብበት መተሳሰብ የሚጎላበት ያዘኑ የሚፅናኑበት፤ ካለን የምናካፍልበት፤ የታረዙት የሚለብሱበት፤ ማዕዳችንን የምናጋራበት ይሁንልን ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጆሀር ባስተላለፉት መልዕክት ትንሣኤ ለሰው ልጆች ሁሉ ከመከራ የመነሳት የተስፋ ምልክት ተደርጎ የሚወሰድ በመኾኑ እኛም አሁን የገጠሙንን የውስጥና የውጭ ችግሮች ተቋቁመን ፈተናዎችን በፅናት ለመሻገር መነሳት ይኖርብናል ብለዋል።

ፍቅርንና አንድነትን በመስበክ ማክበር ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራኒዮ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ዘላለማዊ የሞት መጋረጃን ከማስወገዱም ባሻገር በምድር ላለን ፍቅርን፣ ትህትናን፣ መልካምነትንና ለሌሎች ስንል መስዋዕትነት መክፈልን አስተምሮናል ብለዋል በመልዕክታቸው።

መላው የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ምንም የሌላቸውን ወገኖችን በመርዳት፤ ጧሪ የሌላቸውን አረጋውያን በመደገፍ ያላው ለሌለው በማካፈል በዓሉን ማክበር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።