የሀገር ውስጥ ዜና

በመኖሪያ ቤት ውስጥ የተነሳ የእሳት ቃጠሎ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት አደረሰ

By Feven Bishaw

April 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ወሎ ዞን ኩታበር ወረዳ 05 ቀበሌ ትናንት ምሽት 2 ሰዓት አካባቢ ከመኖሪያ ቤት ውስጥ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ የ80 ዓመት አዛውንት እናት ህይወት አለፈ፡፡

አዛውንቷን ለማዳን ሙከራ ስታደርግ የነበረችው ልጅም መጠነኛ ጉዳት ደርሶባት በህክምና መረዳቷ ተገልጿል።