አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በዋናነት ብሔር እና ሃይማኖትን ሸፋን ያደረገ ጽንፈኝነትና አክራሪነት እያስከተለ ያለውን ጥፋት ለመግታት መንግስት በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ጌታሰው እንዳለው እንደገለጹት ÷ አሁን ላይ ብሔር እና ሃይማኖትን ሽፋን ያደረገ ጽንፈኝነት የሚፈጥረው ችግር እየተባባሰ መጥቷል።