የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የነዳጅ ማከማቻ ተርሚናል በጋራ መገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ

By ዮሐንስ ደርበው

May 05, 2022

ሃገራቱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መስኮች በትብብር መስራት የሚያስችሉ ስምምነቶችን መፈራረማቸው ይታወሳል።

ባለፈው የካቲት ወር ላይም የሃገራቱ አየር መንገዶች ፣ የጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነጻ ቀጠና እና ወደብ ባለስልጣን እንዲሁም የዶራሌ ደረቅ ጭነት ወደብ አገልግሎት በባህር – አየር ሎጅስቲክስ ላይ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸው የሚታወስ ነው።

ሥምምነቱ ቀጠናዊ ትሥሥሩን ይበልጥ በአየር ፣ በየብስ እና በባህር በማሳለጥ በማጠናከር ያላቸውን አጋርነት ያሳድጋል ተብሎለታል፡፡