የሀገር ውስጥ ዜና

ገንዘብ ሚኒስቴር የፋይናንስ ግልፅነትና ተጠያቂነት መመሪያን ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማት ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

By ዮሐንስ ደርበው

May 10, 2022

የፋይናንስ ግልፅነትና ተጠያቂነት መመሪያ ቁጥር 51/2010 ተግባራዊ መደረግ ዘመናዊ የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፥ ከወረዳ ጀምሮ ባሉ መዋቅሮች ተግባራዊ መደረግ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለመልካም አስተዳደር መጎልበት እንደ አንድ መሳሪያ ሆኖ በማገልገል ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

የፋይናንስ ግልፅነትና ተጠያቂነት ተግባራዊ መደረጉ የዜጎች የመሰረታዊ አገልግሎቶች ቅድመ ፍላጎት በዕቅድ እንዲካተት በማድረግ፣ በበጀት አመዳደብና በወጪ አስተዳደር ተሳትፎ፣ በመንግስት ግዥ አፈፃፀምና የኦዲት ግኝት መረጃዎችን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ረገድ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ ግጭትና አለመረጋጋት፣ የፋይናንስ ግልፅነትና ተጠያቂነት መመሪያን በቁርጠኝነት ተግባራዊ ለማድረግ ያላስቻሉ ችግሮች እንደነበሩ መገለጹን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘኘው መረጃ ያመላክታል፡፡