የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ 60 በመቶ የሚሆነውን የመድሀኒትና የህክምና ግብዓት በሃገር ውስጥ እንደምታሟላ ተገለጸ

By Feven Bishaw

May 13, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀጣይ አምስት አመታት ውስጥ ኢትዮጵያ 60 በመቶ የሚሆነውን የመድሀኒት እና የህክምና ግብዓት በሃገር ውስጥ እንደምታሟላ ተገለጸ።

መንግስት በ10 አመቱ የሃገር በቀል ኢኮኖሚን ለማሳደግ በያዘው እቅድ የሃገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪዎች በሃገር ውስጥ የመድኃኒት እና የህክምና ግብዓት እንዲያመርቱ ያሉባቸውን ችግሮች በመፍታት ዘርፉን እንደሚደግፍ ነው የተገለጸው።