አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ 26 ኢንዱስትሪዎች ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው ወደ ስራ መግባታቸውን የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ገለጸ፡፡
የመምሪያው የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ማስፋፊያና ፕሮሞሽን ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ይመር እንደገለጹት፥ በከተማው በክልል እና በፌደራል ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሁም በባንኮችና በመሠረተ ልማት አቅራቢዎች ድጋፍ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል፡፡
በአለባቸው አባተ