አዲስ አበባ፣ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በደቡብ ክልል ከ11 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቋል፡፡
የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የኢንቨስትመንትና ዳያስፖራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደምሰው ባቾሬ እንደተናገሩት ፈቃዱ የተሰጠው በግብርናና ኢንዱስትሪ ዘርፎች የኢንቨስትመንት መመዘኛ ላሟሉ 244 ባለሃብቶች ነው።