አዲስ አበባ፣ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ የደን ልማት ባለስልጣን ገለፀ፡፡
በባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ይማም የተመራ ቡድን ዛሬ ረፋድ ድሬዳዋ ተገኝቶ ከ5 ሚሊየን ብር በላይ የተገነባውን ዘመናዊ የችግኝ ማፍያ ጣቢያና ለዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ እየተካሄዱ የሚገኙ እንቅስቃሴዎችን ጎብኝቷል፡፡