አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 9ኛ ዓመት አስመልክቶ 3ኛው ዙር የ8100A የስልክ መልዕክት የገቢ ማሰባሰቢያ በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በይፋ ተጀምሯል።
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለሀገራችን ህዝብ ኑሮ መሻሻል በአንድነት የዘመትንበት የአድዋ አምሳያ ድላችን፤ የአንድነታችን ተምሳሌት ዳግም አድዋችን ነው ብለዋል።