የሀገር ውስጥ ዜና

የ3ኛው ዙር የ8100A የታላቁ ህዳሴ ግድብ የስልክ መልዕክት የገቢ ማሰባሰቢያ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

March 04, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 9ኛ ዓመት አስመልክቶ 3ኛው ዙር የ8100A የስልክ መልዕክት የገቢ ማሰባሰቢያ በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በይፋ ተጀምሯል።

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለሀገራችን ህዝብ ኑሮ መሻሻል በአንድነት የዘመትንበት የአድዋ አምሳያ ድላችን፤ የአንድነታችን ተምሳሌት ዳግም አድዋችን ነው ብለዋል።