የሀገር ውስጥ ዜና

የመንገድ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከነገ ጀምሮ የቁጥጥር ዘመቻ ይካሄዳል

By Feven Bishaw

May 17, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመንገድ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከነገ ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የቁጥጥር ዘመቻ በአዲስ አበባና በአራት ክልሎች እንደሚጀመር ተገለጸ፡፡

በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የመንገድ ደህንነት እና የመድህን ፈንድ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን በተሰሩ ከጳጉሜ እስከ ጳጉሜ እና መንገድ ለሰው የህዝብ ንቅናቄዎች ከ34 ሚሊየን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጿል።