አዲስ አበባ፣ግንቦት 10፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰብዓዊነት እና የሚዲያ ተቋማት ሚና በሚል የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከሚዲያ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ጸሀፊ አቶ ጌታቸው ታኣ፥ የሚዲያ ተቋማት ቀይ መስቀል ማህበሩ ከአደጋ ምላሽ እስከ ሠብዓዊ ልማት የሚያደርጋቸውን ዘርፈ ብዙ ተግባራት ስልታዊ በሆነ አግባብ እንዲታወቁ በማድረግ ሰብዓዊ ተግባሮችን ማህበራዊና አገራዊ ፋይዳ እንዲያስገኙ የሚያደርገውን ጥረት ከፍ ያደርጉታል ብለዋል፡፡