አዲስ አበባ፣ግንቦት 12፣2014 (ኤፍ ቢሲ) አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ከሳዑዲ የንግድ ምክር ቤቶች ፌዴሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ አጅላን አብዱልአዚዝ ጋር ንግድና ኢንቨስትመንትን ማስፋፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚና የንግድ እንቅስቃሴ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚያስችሉ ስተራቴጅዎች ላይ የመከሩ ሲሆን፥ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ፎረም በማዘጋጀት የሳውዲ የንግድ ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ጉብኝት እንዲያደርጉ በሚቻልባቸው ጉዳዮችም ላይ ተወያይተዋል፡፡