አዲስ አበባ፣ግንቦት 15፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ከኬንያ እና ከታንዛኒያ ጋር በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ሊያፀድቅ መሆኑ ተገለፀ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ አሰግድ ጌታቸው እንደተናገሩት÷ ቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ተደራሽነትን በማስፋት እና ቀጠናዊ ትስስርን ለማጠናከር ከኢትዮጵያ፣ከታንዛኒያ እና ከኬንያ የተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በተጠቀሱት ሀገራት በመዘዋወር እንዲሰሩ የሚያደርግ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል።