የሀገር ውስጥ ዜና

በሶማሌ ክልል በድርቅ የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገለፀ

By Feven Bishaw

May 23, 2022

አዲስ አበባ፣ግንቦት 15፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ገለፁ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር እስቴቨን አውር እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን ተወካይ ዶክተር ማማዱ ዲያን ከተመራ የልኡካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል።