አዲስ አበባ፣ግንቦት 15፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ገለፁ፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር እስቴቨን አውር እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን ተወካይ ዶክተር ማማዱ ዲያን ከተመራ የልኡካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል።