አዲስ አበባ፣ግንቦት 15፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የክትባት ኢኒስቲቲዩት በአፍሪካ ሶስተኛውን ማዕከል በኢትዮጵያ በአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲቲዩት በዛሬው እለት የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ከፍቷል፡፡
በመርሃ ግብሩ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ ፣ በኢትዮጵያ የደቡብ ኮሪያ አምባሳደር ኮንግ ሴኦኬ ፣የዓለም አቀፉ ክትባት ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄሮሚክም፣ በኢትዮጵያ የኮሌራ መከላከልና መቆጣጠር ፕሮጀክት ዋና ተመራማሪ ዶክተር ሲ.ኢቶን ፓርክ የተገኙ ሲሆን የኖርዌይ ጤና ሚኒስትር አማካሪ ዶክተር ቶሬ ጎዳል እና የኖርዌይ ጤና ሚኒስትር አማካሪን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በበይነ መረብ ተሳትፈዋል፡፡