ማዕድን ሚኒስቴር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያስመዘገባቸው ውጤቶች አስቸጋሪ በሆነ ሀገራዊ እና ለዘርፉ ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ መሆኑም በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡
በተለይም የዘርፉ የስራ ሁኔታ ለፀጥታ ስጋትና ችግሮች ቀጥተኛ ተጋላጭ በመሆኑ÷ በአብዛኛው የማዕድን ምርት ባለባቸው አካባቢዎችና ኩባንያዎች በከፊልና ሙሉ በሙሉ ምርት እንዲያቆሙ መደረጋቸውም ተገልጿል፡፡
ያም ሆኖ የወጪ ንግድ ማዕድናትን የምርት መጠን ለማሳደግ ልዩ የድጋፍ፣ የክትትልና የቁጥጥር ስርዓት በተመረጡ አካባቢዎች በመተግበሩ÷ አፈፃፀሙን ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የተሻለ ማድረግ ተችሏል ነው የተባለው።