የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ማላቦ ከተማ ገቡ

By Feven Bishaw

May 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት ኢኳቶሪያል ጊኒ ርእሰ ከተማ ማላቦ ገብተዋል፡፡

በናይጄሪያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፥ ጉብኝቱን አጠናቀው በአፍሪካ ሕብረት ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ነው ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ማላቦ የገቡት፡፡