አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲፋጠን ያሳለፈው ግጭት የማቆም ውሳኔ በትግራይ ብቻ ሳይሆን ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲፋጠን አስችሏል ሲል የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት (ተመድ) ገልጿል።
በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ተጠሪና የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚ ለኢዜአ እንደተናገሩት÷ መንግሥት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ያሳለፈው ውሳኔ የሚፈለገውን ውጤት አስገኝቷል።