የሀገር ውስጥ ዜና

የሰብዓዊ መብቶች ትምህርት በመደበኛ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት እየተሰራ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታወቀ

By Feven Bishaw

May 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰብዓዊ መብቶች ትምህርት በመደበኛ የትምህርት አሰጣጥ ሥርዓት ውስጥ በተደራጀ መልኩ እንዲካተቱ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ያዘጋጀው ሁለተኛው አገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ምስለ-ችሎት ውድድር በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡