የሀገር ውስጥ ዜና

ዋልያዎቹ ከሌሴቶ አቻቸው ጋር በአቻ ውጤት ተለያዩ

By Feven Bishaw

May 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድን ከሌሴቶ አቻው ጋር ባደረገው ሁለተኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይቷል፡፡

በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ዋልያዎቹ በ38ኛው ደቂቃ በዳዋ ሆቴሳ አማካኝነት የመጀመሪያውን ግብ አስቆጥረዋል፡፡