የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ

By Feven Bishaw

June 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳ የሚመሩትና ኢትዮጵያ ታምርት በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ንቅናቄ መድረክ በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የንቅናቄ መድረኩን ቡታጅራ ከተማ የሚገኘውን ደስታ ጋርመንት ፋብሪካ በመጎብኘት ነው ያስጀመሩት፡፡