አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰላምና መረጋጋትን ማረጋገጥ ለሚፈለገው ጠንካራ ቀጠናዊ ትስስር ወሳኝ ሚና እንዳለው የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡
ሃገራዊና ቀጠናዊ የትስስር ጥናት ማዕከል የተሰኘው ተቋም መስራችና የታሪክ ባለሙያ እንዲሁም የአፍሪካ ጉዳዮች ተንታኝ አቶ ኢብራሂም ሙሉ ሸዋ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖርት ጋር ባደረጉት ቆይታ÷ በርካታ አፍሪካውያን ከነጻነታቸው ማግስት ጀምሮ በሃሳብ ደረጃ ሲያራምዱት የቆየው ጠንካራ ማህበረ ኢኮኖሚን የመመስረቱ ጉዳይ በተለያዩ ምክንያቶች መፈተኑን አንስተዋል፡፡