አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ከጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር የትውውቅ እና የውይይት መድረክ አካሂደዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ÷ መሠረታዊ በሆኑ አገራዊ ጉዳዩች ላይ የሚታየውን ስር የሰደዱ የሃሳብ ልዩነቶች እና አለመግባባቶች ለመፍታት ሰፋፊ አገራዊ የሕዝብ ምክክሮችን አካታች በሆነ መንገድ ማስኬድ እንዲቻል መደረጉ ተገቢ ነው ብለዋል።