አዲስ አበባ ፣ የካቲት 27 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ብቁ የሰው ኃይል በማፍራትና ምርምር ከማከናወን ባለፈ የዲፕሎማሲ ኃይል መሆን እንደሚጠበቅባቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ገለፁ።
“የዩኒቨርሲቲ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አንድ እርምጃ ወደፊት ለማራመድ ጠንካራ አመራር”በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።