የሀገር ውስጥ ዜና

በካፋ ዞን በአንድ ጀምበር 10 ሚሊየን የቡና ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር በይፋ ተጀመረ

By Feven Bishaw

June 14, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን በአንድ ጀምበር 10 ሚሊየን የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ ÷ቡና የክልሉ ልዩ እሴት መሆኑን ጠቅሰው የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የክልሉን አርሶአደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስት ይሰራል ብለዋል።