የሀገር ውስጥ ዜና

በህልውና ዘመቻው ለተሳተፉ የጎንደር ከተማ ጤና ባለሙያዎች እውቅና ተሰጠ

By Alemayehu Geremew

June 15, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ በህልውና ዘመቻው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤና ባለሙያዎች ፣ የአምቡላንስ ሹፌሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ዕውቅና ተሰጥቷል፡፡

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባዘጋጀው መርሃ-ግብር የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ዘውዱ ማለደ ÷ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ሀገር በጠላት እንዳትወረር በሙያችሁ ላደረጋችሁት ሀገራዊ አበርክቶ ምስጋና እና ዕውቅና ይገባችኋል ሲሉ ባለሙያዎችን አመስግነዋል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በለጠ ፈንቴ ÷ በህልውና ዘመቻው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ 43 የጤና ባለሙያዎች፣ አምሥት የአምቡላንስ ሹፌሮች እና ሥምንት ጤና ጣቢያዎች ዕውቅና መሠጠቱን ተናግረዋል፡

ኃላፊው አክለውም ሁለት የዕርዳታ ድርጅቶች ፣ የጎንደር ደም ባንክ ፣ ጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፣ ለመድሃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ እና ለግል ጤና ተቋማት ዕውቅና እንዲሁም የዋንጫና የምስጋና የምስክር ወረቀት መሠጠቱንም ጠቁመዋል፡፡

በአበራ መኮንን