የሀገር ውስጥ ዜና

ከ39 ሺህ በላይ ሃሰተኛ የብር ኖት ወደ ባንክ አካውንቱ ሊያስገባ የሞከረ ተጠርጣሪ እጅ ከፍንጅ ተያዘ

By Feven Bishaw

June 21, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ከ39 ሺህ በላይ ሃሰተኛ የብር ኖት ወደ ባንክ አካውንቱ ሊያስገባ የሞከረ ተጠርጣሪ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው ትናንት በክፍለ ከተማው ወረዳ 1 በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ረጲ ቅርንጫፍ ውስጥ ነው፡፡