የሀገር ውስጥ ዜና

የጊምቢቹ ወረዳ ነዋሪዎች ከአንድ ዓመት በፊት በአውሮፕለን አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የሙት ዓመት መታሰቢያ አደረጉ

By Tibebu Kebede

March 08, 2020

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የጊምቢቹ ወረዳ ነዋሪዎች ከአንድ ዓመት በፊት በአውሮፕለን አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የሙት ዓመት መታሰቢያ አደረጉ::

ባለፈው ዓመት መጋቢት 1 የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ከቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ወደ ናይሮቢ ሲያቀና ቱሉ ፈራ እና ሀማ ቁንጥሽሌ ቀበሌዎች አዋሳኝ ላይ ተከሰክሶ የ157 ሰዎች ህይወት ማለፋ ይታወሳል::