የሀገር ውስጥ ዜና

ዩኒሴፍ ለሶማሌ ክልል የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመከላከልና የውሃ አቅርቦትን ለማሻሻል ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ በተባበሩት መንግስት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) የአደጋ ጊዜ ምላሽ አስተባባሪ ፒቴ ማንስፊልድ ከሚመራ ከፍተኛ የለጋሽ ድርጅቶች ልዑካን ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም በክልሉ በተከሰተው የድርቅ አደጋ ተጽዕኖ ሁኔታ፣ በድርጅቱና በክልሉ መንግስት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ዙሪያ መክረዋል።