አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ በተባበሩት መንግስት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) የአደጋ ጊዜ ምላሽ አስተባባሪ ፒቴ ማንስፊልድ ከሚመራ ከፍተኛ የለጋሽ ድርጅቶች ልዑካን ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም በክልሉ በተከሰተው የድርቅ አደጋ ተጽዕኖ ሁኔታ፣ በድርጅቱና በክልሉ መንግስት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ዙሪያ መክረዋል።