የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች በበጋ መስኖ ስንዴ የተሻለ ምርት መገኘቱ ተገለጸ

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዚህ ዓመት በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች በበጋ መስኖ ስንዴ የተሻለ ምርት ማግኘት መቻሉን የየክልሎቹ ግብርና ቢሮዎች አስታወቁ፡፡

የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ አበራ ወርቁ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ÷ በዚህ ዓመት ከ350 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በበጋ መስኖ ስንዴ መልማቱን ጠቁመዋል።