አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያውያንን አብሮነት ሊሸረሽሩ የሚችሉ የጥላቻ ንግግሮችን በሚያሰራጩ አካላት ላይ መንግስት ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አሳሰቡ።
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የጥላቻ ንግግሮችን በሚያስተላልፉ አካላት እና መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፣ ከትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ (ትዴትፓ) እና ከሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ፓርቲ አመራሮች ጋር ቆይታ አድርጓል።