የሀገር ውስጥ ዜና

ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ሄዶ ኮሮና ቫይረስ ተገኘበት የተባለው ግለሰብ ወደ ሀገሪቱ ከተመለሰ ሳምንታትን ያስቆጠረ መሆኑ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

March 10, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ሄዶ ኮሮና ቫይረስ ተገኘበት የተባለው ግለሰብ ወደ ሀገሪቱ ከተመለሰ ሳምንታትን ያስቆጠረ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የጤና ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ሊያ ታደሰ ከትናንት ጀምሮ በማህበራዊ ድረ ገፆች እየተሰራጨ ያለው እና ከኢትዮጵያ እንደ ሄደ ቫይረሱ ተገኘበት በተባለው አሜሪካዊ ጉዳይ ዙሪያ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ማብራሪያ ሰጥተዋል።