የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ ምንም አይነት የነዳጅ እጥረት እንደሌለና የዋጋ ጭማሪ አለመደረጉ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

March 11, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ምንም አይነት የነዳጅ እጥረት እንደሌለ እና የዋጋ ጭማሪ አለማድረጉን የከተማዋ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አመራሮች እና የክፍለ ከተሞች ንግድ ፅህፈት ቤት ሃላፊዎች ሰሞኑን እየታየ ያለውን የነዳጅ ፍላጎት እጥረት በተመለከተ ተወያይተዋል፡፡