አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕዝቡ አንድነቱን ጠብቆ ለአካባቢው ሰላም መስፈን እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር አለሙ ስሜ አሳሰቡ።
ዶክተር ዓለሙ ስሜ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተወከሉበት የአርሲ ዞን መርቲ ወረዳ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ተወያይተዋል።