የሀገር ውስጥ ዜና

ሕዝቡ አንድነቱን ጠብቆ ለሰላም መስፈን እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ዶክተር ዓለሙ ስሜ አሳሰቡ

By Feven Bishaw

July 23, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕዝቡ አንድነቱን ጠብቆ ለአካባቢው ሰላም መስፈን እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር አለሙ ስሜ አሳሰቡ።

ዶክተር ዓለሙ ስሜ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተወከሉበት የአርሲ ዞን መርቲ ወረዳ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ተወያይተዋል።