የሀገር ውስጥ ዜና

ወደ አዳማ ከተማ በመግባት ላይ የነበረ 4ሺህ 603 ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ

By Meseret Awoke

July 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መነሻውን መተሐራ አድርጎ ወደ አዳማ ከተማ በመግባት ላይ የነበረ 4ሺህ 603 ጥይት በቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

1 ሺህ 828 የክላሽ እና 2 ሺህ 775 የብሬን ጥይቶች በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞችና በፌዴራል ፖሊስ አባላት ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ጥይቶችን የያዘው ተሽከርካሪ ለድንገተኛ ፍተሻ እንዲቆም ቢጠየቅም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የፌዴራል ፖሊስ በወሰደው እርምጃ አሽከርካሪውና ግብረ አበሮቹ መኪናውን አቁመው መሰወሩም ነው የተገለጸው።

ወንጀለኞቹ ለጊዜው ቢሰወሩም የፌዴራል ፖሊስና የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮች ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመሆን ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር ለመዋል ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ከጉምሩክ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!