ዓለምአቀፋዊ ዜና

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ካይሮ ገቡ

By Meseret Awoke

July 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ግብፅ ካይሮ ገብተዋል፡፡

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ እንዳስታወቁት ፥ ላቭሮቭ በካይሮ ቆይታቸው ከግብፅ ባለስልጣናት ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ላቭሮቭ የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በይፋ የጀመሩ ሲሆን ፥ በቀጣይም በኢትዮጵያ፣ በኡጋንዳ እና በዲሞከራቲክ ኮንጎ የስራ ጉብኝት እንደሚያከናውኑ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!