የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የምታካሂደው የአካባቢ ጥበቃ ስራ ድንበር ተሻጋሪ ሚና እንዳለው ምሁራን ገለጹ

By Feven Bishaw

July 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ የምታካሂደው የአካባቢ ጥበቃ ስራ ድንበር ተሻጋሪ ሚና እንዳለው የዘርፉ ምሁራን ተናግረዋል፡፡

ዓለም በአየር ንብረት ለውጥ በምትሰቃይበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ዘመኑን የዋጀ መሆኑን ነው ምሁራኑ የገለጹት፡፡