የሀገር ውስጥ ዜና

የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ ግንባታ አፈፃፀም ከ35 በመቶ በላይ የደረሰ

By Feven Bishaw

July 27, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሚያ እና ከጋምቤላ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ ግንባታ አፈፃፀም ከ35 በመቶ በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የመንገድ ግንባታው በትኩረት እየተሰራ መሆኑንና በቀጣይ ዓመት መጀመሪያ ወደ አስፋልት ማንጠፍ ሥራ እንደሚሸጋገር ተገልጿል፡፡