አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ያስተላለፉት መልዕክት ከደረሰብን መከራና ፈተና ይልቅ ለተሰጠን ጸጋ በማመስገን ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት እንዳለብን የሚያሳይ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ዛሬም እንደ ትናንቱ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን፣ እጃችንን ለምስጋና እንዘረጋለን!!” በሚል የምስጋና መልዕክት አስተላለፈዋል።